የሀዘን መግለጫ
የመስሪያ ቤታችን ባልደረባ በሆኑት በወ/ሮ መለሰች መርሻ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሠማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልፃለን!
የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ባልደረባ የነበሩት ወ/ሮ መለሰች መርሻ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።
ቅንና በባልደረቦቻቸው ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት ወ/ሮ መለሰች መርሻ በመስሪያቤቱ ውስጥ በኤክስኪዩቲቭ ሴክሪታሪነት ያገለግሉ ሲሆን በሥራቸው ታታሪና ትጉህ እንዲሁም ሰው አክባሪ ሰራተኛ ነበሩ፡፡
ወ/ሮ መለሰች መርሻ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት በባህርዳር ፈለገ ህይወት ሆስፒታል ለህክምና ቢወሰዱም በነበረባቸው የልብ ህመም ምክንያት ሊሻላቸው ባለመቻሉ በህክምና ላይ እንዳሉ ሰኔ 22/2014 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የቀብር ስነ ስርዓቱም በዛሬው እለት(በ23/10/2014 ዓ.ም) ማሪያም ቤተክርስቲያን ( በመርጡለ ማርያም ከተማ) ይፈፀማል
በወ/ሮ መለሰች መርሻ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቿ ፣ ለሥራ ባልደረቦቿ እና ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን እንመኛለን፡፡
ነፍስ ይማር
የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት