ዜና
በሰሜን ሽዋ ዞን የሚገኘው የአመድ ጉያ በግ ብዜትና ዝርያ ማሻሻያ ማዕከል በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ዘረፋና ወድመት ደርሶበታል፡፡
አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሰሜን ሽዋ ዞን በቆየባቸው ጊዜያት የአመድ ጉያ በግ ብዜትና ዝርያ ማሻሻያ ማዕከልን ዘርፏል ፣ ንብረቶችን አውድሟል
አሸባሪው ቡድን በዞኑ በቆየባቸው ጊዜ ካወደማቸውና ከዘረፋቸው ተቋማት መካከል አንዱ የአመድ ጉያ በግ ብዜትና ዝርያ ማሻሻያ ማዕከል ነው፡፡ ለዝርያ ማሻሻያ የሚውሉ በጎችን አርደው በልተዋል ፣ የበጎች መጠለያና ቢሮዎችን አቃጥለዋል ፣ ኮምፒውተሮች ፣ የተለያዩ ተሸከርካሪዎች እና የበጎች መኖ ጨምሮ በርከት ያሉ ለማዕከሉ አገልግሎት የሚውሉ ንብረቶች በአሸባሪው ቡድን ተዘርፈዋል ፣ መውስድ ያልቻሉትን አቃጥለውታል፡፡