ዜና
በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኘው የኮምቦልቻ እንስሳት በሽታ ቅኝት ጥናትና ምርምር ላብራቶሪ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ዘረፋና ወድመት ደርሶበታል፡፡
አሸባሪው የህወሓት ቡድን በደቡብ ወሎ ዞን በቆየባቸው ጊዜያት የኮምቦልቻ እንስሳት በሽታ ቅኝት ጥናትና ምርምር ላብራቶሪ ዘርፏል ፣ ንብረቶችን አውድሟል
በምስራቅ አማራ ላሉ ወረዳዎች የእንስሳት በሽታ ቅኝት ጥናትና ምርምር ስራዎችን ይጠቀምባቸው የነበሩ ንብረቶችን ዘርፈዋል ፣ አውደመዋል
የቢሮ መስኮትና በሮች ተሰባብረዋል ፣ ኮምፒውተሮች እና ማይክሮስኮፖች ወድመዋል ፣ የተለያዩ የእንስሳት መድሐኒቶች እና መሳሪያዎች ተዘርፈዋል መውሰድ ያልቻሉትን አውደመውታል፡፡