ዜና
አሸባሪው ህውሓት በኮምቦልቻ ዶሮ ሃብት ልማት ኢንተርፕራይዝ ላይ ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት አድርሷል
አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ከተማ በቆየባቸው ጊዜያት የኮምቦልቻ ዶሮ ሃብት ልማት ኢንተርፕራይዝን ዘርፏል ንብረቶችን አውድሟል በተሰራው ጊዜያዊ ግምትም ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ንብረቶች ወድመዋል ፡፡
ü ለዶሮ እርባታ አገልግሎት የሚውሉ ከ15067 በላይ የእርባታ ዶሮዎች ታርደው ተበልቷዋል
ü ለእርባታ አገልግሎት የሚውል ከ100ሽህ በላይ የዶሮ እንቁላል ተበልቷል መብላት ያልቻሉትን አውድመውታል
ü ከ 12000 በላይ የእርቢ እጫጭቶችን ገሏል
ü 1 ትልቅ ጀነሬተር እና 2 ትራክተሮችን አውድሟል
ü 1 ሚኒባስ መኪና ፣ 16 ዲስክ ቶፕ ኮምፒዩተር ፣ 8 ፕሪንትረ ፣ 4 ላፕቶፕ ዘርፏል
ü 7 የጫጩት ማስፈልፈያ ማሽን ፣ 6 እንቁላል ማስታቀፊያ ማሽን ፣ ከ300 በላይ የእንቁላል መጣያ ጎጆ ፣ 2018 የእንቁላል ትሪ እና 82 የዶሮ እና የጫጩት ማጓጓዣ ኩብችን አውድሟል
የዶሮ እርባታ ኢንተርፕራይዝን ከአሁን በፊት ከ15067 በላይ የእርባታ ዶሮዎች የነበሩት ሲሆን በዚህም በየሳምንቱ ከ15ሽህ እስከ 25ሽህ የእርባታ እጫጩቶችን እያስፈለፈለ ለአካባቢው ማህበረሰብ እና በዶሮ ሃብት ልማት ስራ ለተደራጁ ወጣቶች ያሰራጭ ነበረ ፡፡