ዜና 

የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ EAAP በተባለ ኘሮጀክት በክልሉ በሚገኙ 6 ወረዳዎች ለ6 ኢንተርኘራይዞችን ለእያንዳንዱ 1.4 ሚሊዮን ብር ደጋፍ ተደረገ ፡፡

ATA 2014 (7)የአማራ ክልል እንስሳት እና ዓሣ ሃብት ልማት ጽ/ቤት የክልሉን የንብ ሀብት ልማት ለማዘመን እና አናቢውን ተጠቃሚ ለማድረግ በስልጠና፣ በግብዓት አቅርቦትና ድጋፍና ክትትል በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ በተሰሩ ስራዎችም አበረታች ውጤቶች ተመዝገበዋል፡፡ ጽ/ቤቱ የሚሰራቸው ስራዎች በመደገፍ ኘሮጀክቶች ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡ከነዚህ ኘሮጀክቶች ውስጥ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ EAAP የተባለ ኘሮጀክት በክልሉ በሚገኙ 6 ወረዳዎች 6 ኢንተርኘራይዞችን ለእያንዳንዱ 1.4 ሚሊዮን ብር በመደገፍ በስልጠና በግብዓት አቅርቦትና መሠረተ ልማቶችን በማሞላት የንብ ሀብት ልማትን ለማዘመን የሚሰራውን ስራ ሲደግፉ ቆይተዋል፡፡ ኘሮጀክቱ የማጠቃለያ ስራ ርክክብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በ 29/03/2014 በዳንግላ ከተማ የመስክ ጉብኝት እንዲሁም በ 30/03/2014 በባህር ዳር ከተማ ኘሮጀክቱ በቆይታው የሰራቸው ስራዎችና በቀጣይ እንዴት ማስቀጠል እንደሚገባ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡ በምክክር መድረኩ የተገኙ ተጠቃሚዎችና ባለድርሻ አካላትም በቀጣይ ስራውን ለማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ በስፋት ተወያይተው የጋራ መግባባት በማድረግ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

ATA 2014 (18)

ATA 2014 (19)

ATA 2014 (20)

ATA 2014 (21)

ATA 2014 (1)

ATA 2014 (8)

ATA 2014 (11)

ATA 2014 (12)

ATA 2014 (9)

ATA 2014 (10)

ATA 2014 (15)

ATA 2014 (13)

ATA 2014 (14)

ATA 2014 (16)

ATA 2014 (17)

ATA 2014 (2)

ATA 2014 (3)

ATA 2014 (4)

ATA 2014 (5)

ATA 2014 (6)

ATA 2014 (7)

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5

download

 

 

Copyright©2022-ANRS Livestock Resources Development & Promotion Agency. All rights reserved! |