ዜና
ለቻግኒ ዳልጋ ከብት ብዜት ማዕከል ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጣና ተሰጠ፡፡
የክልሉ እንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ29-30/01/2014 ዓ.ም በእንጅባራ ከተማ ለቻግኒ ዳልጋ ከብት ብዜትና ጥበቃ ማዕከል ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አካሄደ ፡፡ ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኤጀንሲው ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ፈንቴ ቢሻው ሲሆኑ ኃላፊው በመክፈቻ ንግግራቸው ማዕከሉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን እያባዙ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨትም ሆነ ንጹህ የፎገራ ዳልጋ ከብት ዝርያዎችን ጠብቆ ከማቆት አንጻር ትልቅ ኃላፊነት የተጣለበት መሆኑን በመግለጽ ይሁን እንጅ ማዕከሉ የተጣለበትን ተግባርና ሃላፊነት በሚፈልገው መጠን አሟልቶ በመፈጸም እረገድ ውስንነቶችን ያሉ መሆኑን ሃላፊው ገልጸው ይህን ስልጠና በሰራተኞች ዘንድ የሚታየውን የክህሎት ክፍተት በመቅረፍ ለቀጣይ ስራ ውጤታማነት አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል፡፡
በስልጠናው ሰልጣኞች የዳልጋ ከብት አያያዝና እንክብካቤ በተመለከተ ከእንስሳት እርባታ እና ጤና አንጻር ሊተኮርባቸው የሚገቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ትኩረት ሰጥቶ በተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልቶችን በመወያየት ለቀጣይ ስራዎች አቅም የሚሆን ግንዛቤ ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የቻግኒ የዳ/ከብት ዝርያ ማሻሻል እና ብዜት ማዕከል የዝርያ ማሻሻልና ጥበቃ የቀጣይ ተግባራት አቅጣጫ በአቶ አህመድ አልቃድር.pptx
የዳ/ ከብት ጤና አጠባበቅ ዙሪያ ለቻግኒ የብዜት ማዕከል ባለመያዎች እና ተንከባካቤዎች የተዘጋጀ ስልጠና በዶ/ር ታምሩ ተሰማ.pptx
የቻግኒ ዳልጋ ከብት ብዜት ዝርያ ማሻሻያ ማዕከል ሪፖርት በአቶ ፈንታሁን.pptx