ዜና 

የአለም የወተት ቀን በደማቅ ሁኔታ በአገር አቀፍ ደረጃ በአማራ ክልል ተከበረ፡፡

milk day 2013 (16)በአለም ለ21ኛ ጊዜና በኢትዮጵያ ለ5ኛ ጊዜ በፈረንጆች አቆጣጠር በየአመቱ June 1 በሃገራችን ግንቦት 24 የሚከበረው አለም አቀፍ የወተት ቀን “ቀንዎን በአንድ ብርጭቆ ወተት ይጀምሩ” በሚል መሪ ቃል በአማራ ክልል በዳንግላ እና በባህር ዳር ከተማ በመስክ ጉብኝትና በፓናል ውይይት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ፡፡

በበአሉ የኢፊድሪ ግብርና ሚኒስቴር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ፍቅሩ ረጋሳ ፣የብሄራዊ ዝርያ ማሻሻያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አስራት ቴራ እና ጥሪ የተደረገለቸው ከክልሎች ፣ ከዩንቨርስቲዎች እና ከምርምር ተቋማት የተገኙ የስራ ሃላፊዎች ፣ ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል፡፡

በመስክ ጉብኝቱ የዳንግላ ወረዳ ዋና ከተማ አስተዳደር ወ/ሮ ንፁህ ሽፈራው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የክልሉ እንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ደበበ አድማሱ የበዓሉን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ጉብኝቱን አስጀምረዋል ፡፡

በመስክ ጉብኝቱ ሞዴል የሆኑ ሁለት የአርሶ አደር የወተት ላም እርባታ ጣቢያዎች እና ሕይወት የወተት ግብይት ህብረት ስራ ማህበር የስራ እንቅስቃሴ ተጎብኝቷል ፡፡

የመስክ ተሳታፊዎችም በጉብኝቱ ወቅት በአዩት ስራ እጅግ መደሰታቸውን በውይይቱ ወቅት በስፋት አንስተው አስተያየት ሰጥተዋል ፡፡

በመጨረሻም የተሻለ አፈፃፀም ላላቸው 6 የወተት ላም አርቢዎች ከዝገት ነፃ የሆነ 10 ሊትር የሚይዝ የወተት ማጓጓዣ እቃዎች በማበረታቻነት ተበርክቷል ፡፡

የመስክ ጉብኝቱም በዚህ መልኩ ከተጠናቀቀ በኃላ በፓናል ውይይቱ በወተት ሃብት ልማት ላይ የሚያተኩር አለምአቀፋዊ እና አገራዊ ፁሁፎች ቀርበው በተሳታፊው ሰፊ ውይይት ተደርጎ የእለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡milk day 2013 (47)

milk day 2013 (2)

milk day 2013 (43)

milk day 2013 (7)

milk day 2013 (8)

milk day 2013 (11)

milk day 2013 (9)

milk day 2013 (30)

milk day 2013 (28)

milk day 2013 (26)

milk day 2013 (32)

milk day 2013 (35)

milk day 2013 (45)

milk day 2013 (22)

milk day 2013 (18)

milk day 2013 (17)

milk day 2013 (19)

milk day 2013 (15)

milk day 2013 (36)

milk day 2013 (39)

milk day 2013 (42)

milk day 2013 (49)

 

 

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5

download

 

 

Copyright©2022-ANRS Livestock Resources Development & Promotion Agency. All rights reserved! |