ዜና 

የእንስሳት እና ዓሳ ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የ3ኛው ሩብ ዓመት የዋና ዋና ስራዎች አፈፃፀም ገመገመ፡፡

LFSDP Third Quarter riport (11)በመድሩኩ የዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈፃፀም በሪፖርት ከመቅረቡ በተጨማሪ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የሆኑ ሴክተር መ/ቤቶች በሩብ አመት ያከናወናቸውን ስራዎች በሪፖርቱ አቅርበዋል ፡፡ በቀረበው ሪፖርት ቤቱ በስፋት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን የቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡

  • በሌቭል 1 ደረጃ ያሉ ተጠቃሚዎች ውጤታማ ከማድረግ አንፃር የእንስሳት ሃት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ተቋም ከእርባታ እና ከጤና አንፃር የሚሰሩ ስራዎችን በመለከተ ችግር ፈች ድጋፍ እንዲያደርግ፡፡

 

  • በንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በኩል ከግብይት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን በተመለከተ በየአካባቢው የሚመረተውን የምርት መጠን ከእንስሳት ሃብት ተቋም መረጃ በመውሰድ የገበያ ትስስር መፍጠር እንዳለበት አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡
  • የማህበራት ማደራጃ ፣አካባቢ ጥበቃ ፣ ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም መሬት አስተዳደር ከዚህ በፊት በየተቋማቸው እንዲሰሩ ተለይተው የተሰጡ ስራዎችን በቀጣይ ሩብ አመት አጠናቀው ሰርተው እንዲመጡ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
  • በወረዳ ደረጃ የተገዙ ግብዓቶች ወደ ቀበሌ ስለ መውረዳቸው ፣ የሚገቡ ግብዓቶች በስፔኩ መሰረት ስለመግባታቸው እንዲሁም ወደ ስራ የገቡ የጋራ ፍላጎት ቡድኖች የተቀመጠውን ስታንዳርድ አግኝተው ወደ ስራ መግባታቸውን በተመለከተ ከኤጀንሲው ኮሜቲ ተቋቁሞ ወደ ታች ወርዶ የማጣራት ስራ እንዲሰራ፡፡
  • በደረጃ 2 ድጋፍ ለሚደረግላቸው ማህበራት ሁሉም ተቋማት በድርጊት መርሃ ግብሩ የተሰጣቸውን ስራ በተቀመጠው ጊዜ እንዲያጠናቅቁ፡፡
  • የማደራጃ ማህበራት 80 የጋራ ፍላጎት ቡድኖችን አባል ማድረጋቸውን እንዲያረጋግጥ፡፡
  • መሬት ሳይኖራቸው በማህበር ደረጃ የተደራጁ ማህበራት ተለይተው በአጭር ጊዜ መሬት የሚያገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች ፡፡
  • የፕሮጀክቱ ስራዎች የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ ይደረግ፡፡
  • ከግዥ አንፃር የሁሉም ወረዳዎች የግዥ አፈፃፀም ከቀሪ ጊዜያት አንፃር ሲገመገም ያለበት ደረጃ ችግር ያለበት በመሆኑ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ ተደርጎ በቀሪ ጊዜያት እንዲጠናቀቅ ይደረግ የሚሉ የቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡

 LFSDP Third Quarter riport (1)

LFSDP Third Quarter riport (8)

LFSDP Third Quarter riport (10)

LFSDP Third Quarter riport (9)

LFSDP Third Quarter riport (4)

LFSDP Third Quarter riport (5)

LFSDP Third Quarter riport (6)

LFSDP Third Quarter riport (7)

LFSDP Third Quarter riport (3)

 

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5

download

 

 

Copyright©2022-ANRS Livestock Resources Development & Promotion Agency. All rights reserved! |