ዜና
የደቡብ ጎንደር ዞን እንስሳት ሃብት ልማት ተ/ጽ/ቤት የ2012 በጀት ዓመት የዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2013 እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ
የደቡብ ጎንደር ዞን እንስሳት ሃብት ልማት ተ/ጽ/ቤት የዞኑ ክፍተኛ አመራሮች፤ የወረዳ አስተዳዳሪዎችና የድርጀት ጽ/ቤት ሃላፊዎች፤ በዞኑ እንስሳት ሃብት ልማት ላይ የሚሰሩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የወረዳ ተ/ጽ/ቤት ሃላፊዎችና ቡድን
መሪዎች እንዲሁም የአዳቃይ ቴክኒሻን በተገኙበት በቀን 10/02/2013ዓ.ም በአዲስ ዘመን ከተማ የ2012 በጀት ዓመት የዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2013 እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ መድረኩ በዞኑ ክፍተኛ አመራሮች የተመራ ሲሆን በመድረኩ የተሻሉ አፈፃፀም ላላቸው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤ ወረዳዎች እና አዳቃይ ቴክኒሻያኖች እውቅና እና የማበረታቻ የምስክር ወረቀት ተሠጥቷል ፡ ፡