ዜና

የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ልማት ኘሮጀክት የ2013 እቅድ የስትሪንግ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

 

የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ልማት ኘሮጀክት የ2012 በጀት አመት የዋና ዋና ስራዎችን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2013 ዓም እቅድ ትውውቅየስትሪንግ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት በቀን 22/01/2013 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ አካሄደ፡፡

ኘሮጀክቱ በ2012 በጀት አመት በወተት ሃብት ልማት፣ በቀይ ስጋ፣ በዶሮ ሀብት ልማት እና በሣ ሃብት ልማት በአርሶ አደር እና በተደራጁ ወጣቶች ዙሪያ የተሰሩ የፊዚካል ስራዎችን ከፋይናንስ አፈፃፀሙ ጋር በዝርዝር በሪፖርት ያቀረበ ሲሆን የስትሪንግ ኮሚቴ አባላትም በቀረበው ሪፖርት በስፋት ከተወያዩ በኃላ የሚከተሉትን ዋና ዋና ገንቢ አስተያየቶች አስቀምጠዋል፡፡

 

• ኘሮጀክቱ ከኮቪድ ጋር ያለውን ወቅታዊ ችግር ተቋቁሞ የ2012 በጀት አመት እቅድን 94% መፈፀም መቻሉ ጥሩ መሆኑንና በቀጣይ ከዚህ በበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት

• ኘሮጀክቱ ዘርፍን ለማዘመን ለወጣቶችና ሴቶችን የስራ ዕድል ለመፍጠር ፋይዳው ትልቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በተጀመረዉ አግባብ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት

• በየደረጃው ያለው ስትሪንግ እና ቴክኒክ ኮሚቴ በመደበኛ ጊዜ ተግባሩን እየገመገመ ከመሄደ አንፃር ያለው ሁኔታ ጥሩ ነው፡፡ በቀጣይም ቢጠናከር

• የሪፖርት አቀራረብ ጥሩ ነው በቀጣይ በአፈፃፀም የተሻሉና ችግር ያለባቸውንም ለይቶ ቢያቀርብ የበለጠ ለግምገማ አመች እንደሚሆን፡፡

• በአንድ የፍላጎት ቡድን የሚመደበው በጀት አናሳ ነው በቀጣይ ቢታይ የሚሉ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በዚህ ዙርያ የሚመለከታቸዉ የስራ ሀላፊዎች በቂ ማብራሪያ በመስጠት የጋራ ግንዛቤ ተፈጥሯል፡፡ በእለቱም የ2013 እቅድ ቀርቦ ዉይይት ከተደረገበት በኋላ እቅዱ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5

download

 

 

Copyright©2022-ANRS Livestock Resources Development & Promotion Agency. All rights reserved! |