ዜና

የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከሴፍ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በቀን 11/02/2012 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ የወተት ቀን አከበረ፡፡

milkday01የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከሴፍ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በቀን 11/02/2012 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ የወተት ቀን አከበረ፡፡ በበአሉ ጥሪ የተደረገላቸዉ የክልል፣የዞን እና የወረዳ ተሳቴፊዎች እና የዳንግላ ከተማ 1ኛ ደረጃ ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡ በአሉን አስመልክቶ የፕሮጀክቱ ሀላፊ አቶ ደስታ ዳመና እንደገለጹት ሴፍ ፕሮጀክት በአማራ ክልል በ2 ዞኖች በምእራብ ጎጃምና በአዊ ብ/አ/ዞን በሚገኙ 4 ወረዳዎች የወተት ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ እና ገቢን በመጨመር በሴቶችና

ወንዶች ፍትሀዊ

ሀብት ተጠቃሚነት ላይ አልሞ የሚሰራ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሀላፊዉ አክለዉም የወተት ቀን በአልን በተማሪዎች ምገባ መልክ ማካሄድ ያስፈለገበትን ሁኔታ በዝርዝር ለታዳሚዎች አስረድተዋል፡፡ በመቀጠልም ለበአሉ ተሳታፊዎች እና ለተማሪዎች የወተት ምገባ ስነስርአት ከተካሄደ በኋላ በወተት ሀብት ልማት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ በኤጀንሲዉ በኩሉ አጭር መነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ዉይይት በማድረግ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡

milkday03

milkday02

milkday04

milkday08

milkday07

milkday06

 

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5

download

 

 

Copyright©2022-ANRS Livestock Resources Development & Promotion Agency. All rights reserved! |