ዜና
ሞየሽ (MOYESH) የተባለ ፕሮጀክት በ10/05/2012ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ የዉይይት መድረክ አካሄደ፡፡
ሞየሽ (MOYESH) የተባለ ፕሮጀክት በ10/05/2012ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ከፌደራል እስከ ወረዳ የሚመለከታቻቸዉ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ፕሮጀክቱ በሚሰራቸዉ ስራዎችና በቀጣይም በየደረጃዉ ካለዉ መንግስት አካላት ጋር ፕሮጀክቱን ዉጤታማ ለማድረግ በቅንጅት መሰራት ባለባቸዉ ጉዳዮች ዙርያ የዉይይት መድረክ አካሄደ፡፡ በመድረኩም በቀጣይ በፕሮጀክቱ ሊሰሩ የታሰቡ ስራዎች ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ዉይይቱንም የፌደራል ግብርና ሚኒሰቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ገብረ እግዚአብሄር የአማራ ቴክኒክና ሙያ ቢሮ ሀላፊ አቶ ሻንበል እንዲሁም የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ አቶ ደበበ አድማሱ መርተዉታል፡፡
ዜና
የከልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ EIF ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ09/05/2012 ዓ.ም በምእራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ የንብ ዉጤቶች ፌስቲቫል እና የፓናል ዉይይት አካሄደ፡፡
የከልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ EIF ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ09/05/2012 ዓ.ም በምእራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ የንብ ዉጤቶች ፌስቲቫል እና የፓናል ዉይይት አካሄደ፡፡ በ ፌስቲቫሉ ቁጥራቸዉ ከ 20 የማያንሱ የ4 ወረዳ አናቢ ማህበራት የማርና ሰም ምርታቸዉን ለእይታና ለገብያ አቅርበዋል፡፡ በእለቱም ተጣርቶ የታሸገ 1 ኪሎግራም ማር በ250 ብር ተሸጥዋል፡፡ ከፌስቲቫሉ በተጨማሪ የአናቢ ማህበራትን የስራ እንቅስቃሴ በመስክ ምልከታ በማድረግ ፕሮጀክቱ በዞኑ ከንብ ሀብት ልማት አንጻር ያከናወናቸዉን ስራዎች እና የወጣቶችን
ዜና
የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ልማት ፕሮጀክቱ የዘርፉን ልማት ለማዘመን አጋዥ የሆኑ 17 ተሸከርካሪዎችን ለ15 ወረዳዎች እና ለ2 የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪዎች የቁልፍ ርክክብ ተደርገ፡፡
የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት በክልላችን በ15 ወረዳዎች በ2011 በጀት አመት ስራ የጀመረ ሲሆን ፕሮጀክቱ በስጋ ፣በወተት፣በደሮ እና በአሳ ሀብት ልማት የተሰማሩ የህብረተሰብ ከፍሎችን እና በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራትን በስልጠና እና በግብአት በመደገፍ ዉጤታማ ና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰራ ፕሮጀክት ከመሆኑ በተጨማሪ ፕሮጀክቱ በዘርፉ የሚሰሩ ተቋማትን በስልጠና እና በግብአት ማጠናከርን አላማ አድርጎ ወደ ስራ የገባ ፕሮጀክት ነዉ፡፡ ፕሮጀክቱ የዘርፉን ልማት ለማዘመን አጋዥ የሆኑ 17 ተሸከርካሪዎችን ለ15 ወረዳዎች እና ለ2 የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪዎች
ዜና
የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ scaling up of honey production and fair trade in Ethiopia ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ17/04/2012 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ የንብ ሀብት ልማት ኢግዚቪሽንና ፓናል አካሄደ፡፡
የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ scaling up of honey production and fair trade in Ethiopia ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ17/04/2012 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ የንብ ሀብት ልማት ኢግዚቪሽንና ፓናል አካሄደ፡፡ በኢግዚቪሽኑ ቁጥራቸዉ ከ15 ያላነሱ የንብ አናቢ ማህበራት የማርና ሰም ምርታቸዉን ለእይታ አቅርበዋል፡፡ በኢግዚቪሽኑም ጥሪ የተደረገላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች በመገኘት በአናቢ ማህበራት የቀረቡ ምርቶችን እንዲቀምሱ ተደርጓል፡፡ ግብይትም ተፈጽሟል፡፡ በፓናል ዉይይቱም ቁጥራቸዉ ከ100 ያላነሱ ተሳታፊዎች ተሳትፈዋል፡፡በዉይይቱም በየሽ ፕሮጀክት ከንብ ሀብት ልማት አንጻር በአዊ ብ/አስ ዞን በ3 ወረዳዎች የተሰሩ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን
ዜና
የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ዘርፍ ለክልሎች የ122 ተሸከርካሪዎች ድጋፍ አደረገ::
በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፉን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግና መንግስት በእንስሳት ልማትና ሽግግር ረገድ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለመደገፍ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ከእነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ ግንባር ቀደም የሆነው የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ሴክተር ፕሮጀክት የፕሮጀክቱን ዓላማ ለማሳካት የሚረዳ ተሸከርካሪዎችን ፕሮጀክቱ ለሚሰራባቸው ክልሎች አበርክቷል፡፡በ106 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ከአለም ባንክ በተገኝ የገንዘብ ድጋፍ 122 ተሸከርካሪዎች ለርክክብ ዝግጁ መደረጋቸውን ነው የግብርና ሚኒስቴር የገለፀው፡፡
ዜና
በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ድጋፍ ተደራጅተው በንብ ማነብ ስራ የተሰማሩ ወጣቶች የስራ እንቅስቃሴ
ዜና
እድገት ለህብረት የንብ አናቢዎች ማህበር የሚገኘው በዋግ/ብ/አስ ዞን ሰቆጣ ወረዳ 03/ሃሙሲት ቀበሌ ሲሆን ማህበሩ ኡሁን ላይ ወንድ 7 ሴት 3 በድምሩ 10 አባላትን በመያዝ በ23 ዘመናዊ ቀፎዎች የንብ ማነብ ስራ እየሰሩ ይገኛል::
የአማራ ክልል ለንብ ሃብት ልማት ምቹ ሰነ-ምህዳር ያለው ክልል ነው ፡፡ እንደ ማዕከላዊ ስታስቲክስ 2017/2018 መረጃ መሰረት በክልሉ 1.15ሚሊዮን ያክል የንብ መንጋ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳ በክልላችን ሰፊ የሆነ የንብ ሃብት ልማት ቢኖርም ንብ አናቢው የህብረተሰብ ክፍል አሁንም ድረስ በሚከተለው ኋላቀር የንብ ማነብ ዘዴ ህብረተሰብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም ሳያገኝ ቆይቶል ፡፡ የክልሉ እንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ንብ አናቢው የህብረተሰብ ክፍል ሳይንሳዊ ዘዴ ተጠቅሞ የንብ ማነብ ስራ እንዲሰራ በስልጠና ፤ በግብዓት አቅርቦትና በድጋፍና ክትትል በርካታ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል ፡፡
ዜና
ጥምቀተ ባህር የንብ አናቢዎች ማህበር የሚገኘው በሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ ሹምሻ ቀበሌ ሲሆን ማህበሩ ኡሁን ላይ 8 አባላትን በመያዝ በ37 ዘመናዊ ቀፎዎች የንብ ማነብ ስራ እየሰሩ ይገኛል::
የአማራ ክልል ለንብ ሃብት ልማት ምቹ ሰነ-ምህዳር ያለው ክልል ነው ፡፡ እንደ ማዕከላዊ ስታስቲክስ 2017/2018 መረጃ መሰረት በክልሉ 1.15ሚሊዮን ያክል የንብ መንጋ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳ በክልላችን ሰፊ የሆነ የንብ ሃብት ልማት ቢኖርም ንብ አናቢው የህብረተሰብ ክፍል አሁንም ድረስ በሚከተለው ኃላ ቀር የንብ ማነብ ዘዴ ህብረተሰብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም ሳያገኝ ቆይቶል ፡፡ የክልሉ እንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ንብ አናቢው የህብረተሰብ ክፍል ሳይንሳዊ ዘዴ ተጠቅሞ የንብ ማነብ ስራ እንዲሰራ በስልጠና ፤ በግብዓት አቅርቦትና በድጋፍና ክትትል በርካታ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል ፡፡