የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እንስሳት ሃብት ልማት ማስፈፊያ ኤጀንሲ ለመላው የአገራችን ህዝቦች እንኳን ለ2013 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ አመቱ የሰላም ፤ የጤና ፤ የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል::
ዜና
በቀረበው የ2012 በጀት አመት የዋና ዋና ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2013 እቅድ ትዉዉቅ መድረክ ዙሪያ የዞን ፡ የማዕከላት እና የኤጀንሲው ሃላፊዎች የሰጡት አስተያየት
ዜና
የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ26—27/12/2012 በባህርዳር ከተማ የ2012 በጀት አመት የዋና ዋና ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2013 እቅድ ትዉዉቅ አካሄደ፡፡
የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ26—27/12/2012 በባህርዳር ከተማ የዞን ሀላፊዎችና ቡድን መሪዎች ፣የማአከላት ሀላፊዎች፣የ 3ቱ ከተማ አስተዳደርና ሀላፊዎችና ቡድን መሪዎች እንዲሁም የኤጀንሲዉ ስራ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት የ2012 በጀት አመት የዋና ዋና ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2013 እቅድ ትዉዉቅ አካሄደ፡፡በመድረኩ የዋና ዋና ስራዎች አፈጻጸም ማለትም፡- የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል፣ የእንስሳት መኖ ልማት፣የእንስሳት ጤና አጠባበቅ ስራዎች እንዲሁም በንብ ሀብት ልማትና በአሳ ሀብት ልማት ስራዎቻችን ዙርያ በአፈጻጸም ረገድ የነበሩ ጥንካሬዎችና እጥረቶች ተለይተዉ በዝርዝር የተገመገሙ እና በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት በሚቻልበት ሁኔታ የጋራ ግንዛቤ የተየዘ ሲሆን፡፡ በመጨረሻም የ2013 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ ሰፊ ዉይይት ከተደረገበት በኋላ የቀጣይ አቅጣጫዎች ተሰጥተዉ ዉይይቱ ተጠናቆዋል፡፡
ዜና
የንብ ሃብት ልማትን ለማዘመን እየተሰሩ ያሉ ስራዎች እና በተሰሩ ስራዎች የህ/ሰቡ ተጠቃሚነት በተለይ ዘርፉ ለወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንፃር ያለው ፋይዳ
በኢትዮጰያ 6,523,969 የሚጠጋ የንብ መንጋ ብዛት እንዳለ የCSA-2010 መረጃ ያሳያል ከዚህም ውስጥ በአማራ ክልል 1,154,094 የንብ መንጋ ብዛት እንዳለ ያሳያል ይህም ከሃገሪቱ የንብ ሃብት ብዛት 17.7% ድርሻ ይኖረዋል ማለት ነው እንዲሁም በ2010 CSA መረጃ መሰረት በአማራ ክልል 1,115,835 ባህላዊ ቀፎ እንዲሁም 5,986 የሽግግር ቀፎ እና 32,273 ዘመናዊ ቀፎ ይኖራል ተብሎ ይገመታል፡፡ የንብ ሀብት ተግባር ከተለያዩ አቅጣጫወች ሲታይ ሁለገብና አስተማማኝ ዘላቂ የሆነ ጥቅም የሚያስገኝ ስራ ነው፡፡ ከጤና አንጻር በመዳህኒትነት የሚያገለግሉ ንጥረ ነገሮችን የያዘና በምግብነትም ከፍተኛ የሆነ የሀይል ምንጭ ሲሆን ፣ ከኢኮኖሚ ጠቀሜታ አንጻር ሲታይ በቀጥታ
ዜና
በቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ አቅራቢያ ለሚገኙ የወተት ህብረት ስራ ማህበራት ድጋፍ ተደረገ ::
በክልሉ የወተት ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ያሉንን ዝርያዎች የውጭ ደም ካላቸውና በወተት ምርታቸው ከታወቁ እንስሳት ጋር በማዳቀል ዝርያቸውን የማሻሻል፤ የእንስሳት ጤና አጠባበቅ ተደራሽትንና ጥራትን የማሳደግ እንዲሁም የተሻሻለ መኖ ልማትን ማስፋፋት ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል፡፡ እነዚህ ተግባራት ተሟልተው በተከናወኑባቸው በርካታ አካባቢዎች የወተት ምርት እድገት በማሳየቱ ወደ ገበያ የሚቀርበው ወተት እየጨመረ መጥቷል፡፡ በመሆኑም በክልላችን 119 የወተት
ዜና
በአማራ ክልል እንስሳት እና ዓሳ ሀብት ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት የተሰሩ ስራዎች በግብርና ሚኒስትር ድኤታው ተጎበኙ::
የእንስሳት እና ኣሳ ሀብት ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት በአማራ ክልል ወደ ስራ የገባዉ በ2011 በጀት አመት ነዉ፡፡ ፕሮጀክቱ የዘርፉን ልማት ለማዘመን ትልቅ አቅም ያለዉ ፕሮጀክት ሲሆን በክልሉ በ 15 ወረዳዎች በ 199 ቀበሌዎች 4110 ወጣቶችንና 16302 አርሶ አደሮችን በቀይ ስጋ ማድለብ፣ በወተት ፣በደሮ እና በዓሳ ሀብት ልማት አደራጅቶ ወደ ስራ አስገብቷል፡፡ፕሮጀክቱ በበጀት አመቱ ከላይ ለተጠቀሱ የህብረተሰብ ክፍሎች ለግብአት መግዣ፣ ለእንስሳት ቤት ግንባታና ማሻሻያ፣ እንዲሁም ለቁሳቁስ መግዣ በድምሩ 135 ሚሊዮን ብር
ዜና
የተከዜ ዓሳ ሀብትን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚያደርሱ ተሽከርካሪዎች ለአራት ወረዳዎች ተሰጡ።
ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 29/2012 ዓ.ም የተከዜ ዓሳን ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ እየተሠራ ነው። በ16 ሚሊዮን ብር ወጭ የተከዜን ዓሳ ሀብት ሳይበላሽ ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚያደርሱ ተሽከርካሪዎች ለአራት ወረዳዎች ተሰጥዋል።በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ጎንደር ዞን ለሚገኙ አራት ወረዳዎች ማለትም ስሃላ ሰየምት፣ ዝቋላ፣ አበርገሌ እና ጠለምት ወረዳዎች ለአካባቢዎቹ ተስማሚ የሆኑና ማቀዝቀዥ ያላቸው አራት ተሽከርካሪዎች ዛሬ ሚያዝያ 29/2012 ዓ.ም ተሰጥቷቸዋል።ተሽከርካሪዎችን ያስረከቡት የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት
ዜና
የአማራ ክልል እንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ የተከዜ ሐይቅ ዓሳ ሃብት ልማትን በማልማትና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ በኩል የተሰሩ ስራዎች፤ ያጋጠሙ ችግሮች እና ችግሮችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የመፍትሄ እርምጃዎች፡፡
- ሞየሽ (MOYESH) የተባለ ፕሮጀክት በ10/05/2012ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ
- የከልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ EIF ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ09/05/2012 ዓ.ም በምእራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ የንብ ዉጤቶች ፌስቲቫል እና የፓናል ዉይይት አካሄደ፡፡
- የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ልማት ፕሮጀክቱ የዘርፉን ልማት ለማዘመን አጋዥ የሆኑ 17 ተሸከርካሪዎችን ለ15 ወረዳዎች
- የክልሉ እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ከ scaling up of honey production and fair trade in Ethiopia ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ17/04/2012 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ የንብ ሀብት ልማት ኢግዚቪሽንና ፓናል አካሄደ፡፡